ገዢው ፓርቲ ብልፅግና፣ አንደኛ ጉባዔውን ከመጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አዳራሽ አካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን የፓርቲው ፕሬዚዳንት ያደረገው ጉባዔው፣ በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተስተናግደውበታል፡፡ አዳራሹ ከሠላሳ ስምንት ዓመታት በፊት በወርኃ ጳጉሜን ‹‹የኢሠፓ ጉባዔ አዳራሽ›› በሚል መጠርያ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ) መሥራች ጉባዔ የተካሄደበት መሆኑ ይታወሳል፡፡ ፎቶዎቹ የብልፅግና ፓርቲ ቀዳሚ ጉባዔ ከፊል ገጽታን ያሳያሉ፡፡
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -
ፌርማታ ፅሁፎች
ትኩስ ፅሁፎች
- Advertisement -
- Advertisement -