Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየዓለም ባንክ የአፍሪካ ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ጋር...

የዓለም ባንክ የአፍሪካ ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተወያዩ

ቀን:

  • በጦርነት ለተጎዱ አካባቢዎች የፋይናንስ ድጋፍ ጥያቄ ላይ ለመወሰን ቀጠሮይዟል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (/) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ከዓለም ባንክ የአፍሪካ ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሆኑት ታኡፊላ ናያማዛቦ ጋር ተወያዩ። 

በዓለም ባንክ በአፍሪካ ለሚገኙ 21 አገሮች ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቦትስዋናዊው ታኡፊላ ናያማዛቦ ካለፈው ሰኞ መጋቢት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ በቆይታቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን ጨምሮ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።

የባንኩ የአፍሪካ ቡድን ኃላፊ ጋር ተገናኝተው ከመከሩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች መካከልም የፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ (/) እና የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ (/) ይገኙበታል።

ባንኩ የኢትዮጵያ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገ የሚገኘውንአገር በቀል የኢኮኖሚ ልማት ፕሮግራምለመደገፍ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ስምምነት የፈጸመ ቢሆንም፣ የፋይናንስ ድጋፉ በተገቢው ጊዜ አለመለቀቁ በመንግሥት ላይ ያስከተለውን ጫና በተመለከተ ከባንኩ የአፍሪካ ቡድን ኃላፊ ጋር ውይይት መደረጉን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል። 

በውይይቱም ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ልማት ዕቅዱ ማስፈጸሚያ የተፈቀደው የፋይናንስ ድጋፍ በፍጥነትና በተሟላ መልኩ መለቀቅ በሚችልበት ሁኔታ ላይ መግባባት እንደተደረሰ ምንጮቹ ገለጸዋል። 

ከዚህ ጉዳይ ባሻገር በኢትዮጵያ በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባትና ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም፣ መንግሥት ባቀረበው የፋይናንስ ድጋፍ ጥያቄ እንዲሁም፣ በድርቅና በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የኢኮኖሚ ተዕዕኖዎች ዙሪያ ባንኩ የሚያደርገውን ድጋፍ በተመለከተ ውይይት መደረጉን ምንጮቹ ገልጸዋል።

በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤት የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ የሆኑት ገሊላ ውድነህ፣ የባንኩ የአፍሪካ ቡድን ዋና አስፈጻሚ በአዲስ አበባ ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ ለሪፖርተር በሰጡት ምላሽ፣ በአሁኑ ወቅት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በሚመሩት የአፍሪካ ቡድን ውስጥ የሚገኙ አገሮችን በመጎብኘት ላይ መሆናቸውን በዋናነት ገልጸዋል።

ኢትዮጵያም የዚሁ ቡድን አንዷ አባል አገር በመሆኗ የተደረገ ጉብኝት ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥትም ጉብኝቱ በዚህ ወቅት እንዲፈጸም ለዋና አስፈጻሚው ግብዣ ማድረጉን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት፣ ከባንኩ የአፍሪካ ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚና በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ዳይሬክተር ጋር በኦሮሚያ ክልል የተጀመሩ የስንዴ ማሳዎችን እንደጎበኙና በዚህም መንግሥት ከውጭ እያስገባ ያለውን የስንዴ ምርት ለመተካት እያደረገ ያለውን ጥረት በአካል መመልከት መቻላቸውን ገልጸዋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ (/)፣ ከባንኩ የአፍሪካ ቡድን ዋና አስፈጻሚ ጋር በነበራቸው ውይይት፣ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገ የሚገኘውን የአሥር ዓመት የኢኮኖሚ ልማት ዕቅድ በተመለከተ ገለጻ ማድረጋቸውን ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

ባንኩ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማት ከሚያደርገው ትብብርና ከሰብዓዊርዳታ ድጋፎቹ ዓይኑን ሊያነሳ እንደማይገባ ሚኒስትሯ በውይይቱ ወቅት በአጽንኦት መናገራቸውን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ (/)፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት፣ ከባንኩ የአፍሪካ ቡድን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋር በአደጋ ጊዜ ምላሽ፣ በመልሶ ግንባታና ማገገሚያ ፕሮጀክቶች፣ በሥነ ምግብ፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤናና ሌሎች ቅድሚያ የሚሰጣቸው ተግዳሮቶችን ለመፍታት የዓለም ባንክ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደመከሩ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይን ጨምሮ በጦርነትና ግጭት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባትና ነዋሪዎችን ለማቋቋም 19 ቢሊዮን ብር በላይ የሚጠይቅ ፕሮጀክት ይፋ ማድረጉን ሪፖርተር በእሑድትሙ መዘገቡ የሚታወስ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ከሚጠይቀው ወጪ 15 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወይም 300 ሚሊዮን ዶላር የሚሆነው ወጪ በዓለም ባንክ እንዲሸፍን መንግሥት የፋይናንስ ድጋፍ ጥያቄውን ለባንኩ አቅርቧል።

ለዚህ የመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋም ፕሮጀክት የፋይናንስ ድጋፍ ጥያቄ ላይ ለመወሰን የዓለም ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ለመጪው ዓርብ መጋቢት 16 ቀን 2014 ዓዓም. ጊዜያዊ ቀጠሮ መያዙን የባንኩ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በጉዳዩ ላይ የጠየቅናቸው የባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ ገሊላ ውድነህ፣ የባንኩ ቦርድ በኢትዮጵያ መንግሥት የድጋፍ ጥያቄ ላይ ለመወያየት ለመጪው ዓርብ የያዘው ቀጠሮ ጊዜዊ መሆኑንና እንደ ሁኔታው ሊለወጥ አሊያም ሊካሄድ እንደሚችል ገልጸዋል።

በቀረበው የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ባንኩ የወከላቸው ባለሙያዎች ባደረጉት የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማኅበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸምን በተመለከተ በተለይም ፕሮጀክቱ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ካለው የፀጥታጋት ጋር የተገናኘ ሥጋት ማንሳታቸውን የባንኩ የግምገማ ሰነድ ያስረዳል።

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...