Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበበይነ መረብ አማካይነት በዓመት 300 ሺሕ ሕፃናት ፆታዊ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው አንድ ጥናት...

በበይነ መረብ አማካይነት በዓመት 300 ሺሕ ሕፃናት ፆታዊ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው አንድ ጥናት አመለከተ

ቀን:

በኢትዮጵያ በበይነ መረብ አማካይነት በሕፃናት ላይ በከፍተኛ መጠን ፆታዊ ጥቃት እንደሚፈጸምና በዓመት 300 ሺሕ የሚደርሱ ሕፃናት ተጠቂ መሆናቸው በጥናት ተመላከተ።

 

በኢትዮጵያ የኢንተርኔትና የሞባይል ስልኮች መበራከት ምክንያት፣ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ የበይነ መረብ ታዊ ጥቃቶችን ለማወቅ ኢንተርፖል፣ ዩኒሴፍና ኢሲፒኤቲ የተባሉ ድርጅቶች ጥናት አድርገዋል።

ጥናቱ ከመጋቢት ወር 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የነበረ መሆኑን፣ በዋናነትም በሕፃናት በተለይ በታዳጊ አገሮች እየደረሰ ያለውን ታዊ ጥቃት የዳሰሰ መሆኑን በኢትዮጵያ የኢሲፒኤቲ (ECPAT) ተወካይ አቶ ያሬድ አሰፋ ተናግረዋል። ስለሕፃናት ጥቃት ሲነሳ በተለይ በኢትዮጵያ በአካል ስለሚደረግ ጥቃት እንጂ በበይነ መረብ ስለሚደርስ ጥቃት ትኩረት አልተሰጠም ብለዋል። 

በዚህም መነሻነት የጥቃቱን መጠንና ጥቃቶቹ የሚስተናገዱበትን የሕግ ጉዳዮች ለመፈተሽ፣ ሦስቱ ተቋማት ለአራት ዓመታት በከተሞች፣ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ጥናት ሲያካሂዱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በጥናቱ 1‚000 ሕፃናት፣ አሥር የመንግሥት አካላት፣ 30 በልጆች ጉዳይ ላይ የሚሠሩ ተቋማትና ግለሰቦች መካተታቸው ተገልጿል፡፡

በጥናቱ ግኝት መሠረት በተለይ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ በኢትዮጵያ ከ12 እስከ 17 ዓመት ዕድሜ ካላቸው የበይነ መረብ ተጠቃሚ ሕፃናት ውስጥ አሥር በመቶ ያህሉ ‹‹ለከፋ›› የበይነ መረብ ወሲባዊ ጥቃት ተዳርገዋል። ይህም ሕፃናቱ በወሲባዊ ተግባራት እንዲሳተፉ በማስገደድና መደለያ ገንዘብ በመስጠት የተፈጸሙ ናቸው ተብሏል። በዚህም መሠረት በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 300 ሺሕ ያህል ሕፃናት በበይነ መረብ አማካይነት ፆታዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ጥናቱ አመልክቷል።

በበይነ መረብ ጥቃት የሚፈምባቸው ሕፃናት የሚደረግላቸውን የግ ከለላ የዳሰሰው ጥናቱ ወሲባዊ ቃት ከደረሰባቸው ሕፃናት ውስጥ ለግ አካላት አቤቱታ ያቀረቡ አለመኖራቸውን የገለጹት አቶ ያሬድ ይህም መደበኛ የአቤቱታ ማቅረቢያ መንገድ ባለመኖሩ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል። በሥርዓቱ ውስም ጉዳዩን ለማስተናገድ የሚያስችል አራርም ሆነ ግንዛቤ ያለው የግ አካል አለመኖሩን በጥናቱ ለማወቅ ተችሏል ብለዋል።

 ፌስቡክና ቴሌግራም በዋናነት የሕፃናት ፆታዊ ጥቃት የሚፈጸምባቸው ማኅበራዊ መገናኛዎች መሆናቸውን ያመለከተው ጥናቱ፣ እስከ 27 በመቶ የሚደርሱ ጥቃቶች በማይታወቁ ሰዎች ጭምር የተፈጸሙ መሆናቸውን አብራርቷል። የሕፃናቱን ምሥል በመጠቀም ማስፈራራትና በገንዘብ መደለል ለጥቃቱ ዋነኛ መንገዶች ሲሆኑ፣ አብዛኛው ጥቃት የሚፈጸመው ሕፃናቱ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል።

በጥናቱ ግኝት መረት በተለይ የፖሊስ አደረጃጀት የበይነ መረብ ጥቃት የሚስተናገድበት አራር እንዲኖረው፣ ባለሙያዎችም በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ እንደሚያስፈልግ አቶ ያሬድ ጠቁመዋል። በተጨማሪም በርዓ ውስጥ ይህንን ድርጊት ለመከላከል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ እንዲካተት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ጥናቱ በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ኬንያና ኡጋንዳን ጨምሮ በ13 አገሮች የተካሄደ መሆኑን፣ ሰባት ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንደተደረገበትም አቶ ያሬድ ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...