Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከስደት ተመላሾችን ለማቋቋም 7.4 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል

ከስደት ተመላሾችን ለማቋቋም 7.4 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል

ቀን:

ከሳዑዲ ዓረቢያ የሚመለሱ ኢትዮጵያዊያንን ለማቋቋም 7.4 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ፣ ከስደት ተመላሾች መልሶ ማቋቋም ኮሚቴ አስታወቀ።

መንግሥት በሳዑዲ ዓረቢያ የነበሩ ስደተኞች ለበርካታ ጊዜያት በእስር ከቆዩ በኋላ ከመጋቢት 21 ቀን 2014 .ም. ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ጀምሯል። በሳዑዲ ዓረቢያ በአጠቃላይ ከ750 ሺሕ ዜጎች እንደሚኖሩና 450 ሺሕ የሚሆኑት በሕገወጥ መንገድ የሄዱ መሆናቸውን፣ የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (አይኦኤም) መረጃ ያመለክታል። መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ ለመለለስ በዕቅድ የያዘው 102 ሺሕ ዜጎችን ሲሆን፣ ይህም ከሰባት እስከ 11 ወራት እንደሚወስድ ተገልጿል።

ከስደት ተመላሾቹ ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች የሚቆዩ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ስድስት ሺሕ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሰባት መጠለያዎች መዘጋጀታቸውን ከስደት ተመላሾች መልሶ ማቋቋም ኮሚቴ ተጠሪ አቶ ተፈሪ ታደሰ ገልጸዋል። ዜጎቹ ከደረሰባቸው ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ሲያገግሙም የራሳቸውን ራ ለማስጀመር የማቋቋም እንደሚከናወን አክለዋል።

መልሶ ማቋቋሙን ለማከናወን በአጠቃላይ እስከ 7.4 ቢሊን ብር እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ ተፈሪ ይህም መንግትን ጨምሮ ከረጂ ድርጅቶችና ከፋይናንስ ተቋማት ለማግት መታቀዱን ዓርብ መጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ.ም. ከፋይናንስ ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር በተደረገበት ወቅት ተናግረዋል።

ገንዘቡ በብድር መልክ ለማቅረብ ቢታሰብም በተለይም ከፋይናንስ ተቋማት ለሚገኘው ብድር እንደ ችግር የሚነሳው የማስያዣና የወለድ ችግር መሆኑን አስረድተዋል። ለዚህም የፋይናንስ ተቋማት የሚሰጡት ብድር በአነስተኛ ወለድ በአፋጣኝ እንዲያቀርቡ ተጠይቀዋል።

የብድር አቅርቦቱን በተመለከተ ለሪፖርተር አስተያየታቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጥቃቅንና አነስተኛ ብድር አቅርቦት ዳይሬክተር ወ/ሮ መልካም በለጠ መንግትም ሆነ ረጂ ድርጅቶች ዋስትና ከገቡ ብድሩን ማቅረብ እንደሚቻል ገልጸዋል።

ለዚህም በተለይ ባንኮች እንደ መፈርት የሚጠይቁት የአዋጭነት ጥናት በመሆኑ ተቀባይነት ያለው የአዋጭነት ጥናት ተደርጎ መቅረብ ይጠበቅበታል ብለዋል። ከስደት ተመላሾችም ሆነ ጥቃቅንና አነስተ ተቋማት ብድር ሲጠይቁ ያለ በቂ ጥናት በመሆኑ ባንኮች ብድሩን ለመስጠት እንደሚቸገሩ የገለጹት ወ/ሮ መልካም ለዚህም መንግትም ሆነ ሌሎች አካላት ደረጃውን የጠበቀ የብድር መጠየቂያ ጥናት በመራት ሊደግፏቸው ይገባል ብለዋል።

የእናት ባንክ የቅርንጫፍ ራ ማስተባበሪያና ብት ማሰባሰብ ዳይሬክተር ወ/ሮ በለምላይ አየነው በበኩላቸው እናት ባንክ ለሴቶች ቅድሚያ ሰቶ የሚራ ባንክ ስለሆነ ከስደት ተመላሽ ለሆኑ ሴቶችም ብድር ለማቅረብ ፈቃደኛ መሆኑን ተናግረዋል። 

ተቀባይነት ያለው የራ ምክረ ሳብ ለሚያቀርቡም ያለ ማስያዣ እስከ 300 ሺ ብር ከእናት ባንክ መበደር እንደሚችሉ ገልጸዋል። በተለያየ መንገድም እስከ 70 በመቶ የሚሆነውን መጠን ለሚያስይዙ ብድር እንደሚቀርብላቸው አክለዋል።

ብድር ከተገኘ በኋላ ወደ ራ ለሚገቡት የመሥሪያ ቦታዎች ክልሎች እንደሚያቀርቡ አቶ ተፈሪ ገልጸው፣ የመሪያ ቦታዎችን ሙሉ ለሙሉ ማቅረብ ካልተቻለ ደግሞ በኪራይ እንደሚጠቀሙና ክፍያውንም መንግት እንዲሸፍን ይደረጋል ብለዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...