Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናምርጫ ቦርድ በወንጀል የጠረጠረውን የኦሮሚያ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲን ፌደራል ፖሊስ እንዲመረምረው ጠየቀ

ምርጫ ቦርድ በወንጀል የጠረጠረውን የኦሮሚያ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲን ፌደራል ፖሊስ እንዲመረምረው ጠየቀ

ቀን:

የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባዔውን አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያቀረበው ሰነድ በሕግ እስከሚጣራ ድረስ መታገዱን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ማክሰኞ መጋቢት 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ በጻፈው ደብዳቤ፣ ፓርቲው ባቀረበው ሐሰተኛ መረጃ ላይ ምርመራ እንዲጀመር ጠይቋል፡፡

ኦነን መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ 541 የጠቅላላ ጉባዔ አባላት መገኘታቸውን ለምርጫ ቦርድ ሪፖርት አድርጎ ስብሰባውን አስጀምሮ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ታዛቢዎች ስብሰባው እየተካሄደ ሳለ ዳግም ቆጠራ ሲያደርጉ 250 አባላት ብቻ መሳተፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ኦነን አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ ምልዓተ ጉባዔ የሚሟላው 500 የጉባዔ አባላት ከተገኙ ነው፡፡ ፓርቲው መጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ 634 የጉባዔ አባላት መታደማቸውን ገልጾ፣ ይህም አስቀድሞ የቦርዱ ታዛቢዎች ካደረጉት ቆጠራ በላይ ነው ብሏል፡፡

ምርጫ ቦርድ ለወንጀል ምርመራ ቢሮ በጻፈው ደብዳቤ፣ ኦነን ሐሰተኛ የተሳታፊዎች ዝርዝርና ፊርማ ማቅረቡን አትቶ፣ አጠራጣሪ ሰነዶች በወንጀል ምርመራ እስኪጣራ ድረስ ፓርቲውን ማገዱን ገልጿል፡፡

የኦነን ኃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሪፖርተር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡

ምርጫ ቦርድ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተነሳ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባዔ እንዲያካሂዱ ማዘዙ ይታወሳል፡፡ ኦነን በአንዳንድ የአሪቱ ክፍሎች የፀጥታ ችግር ስላለ የጠቅላላ ጉባዔ አባላቱ በተጠቀሰው ጊዜ መድረስ እንደማይችሉ ለምርጫ ቦርድ አሳውቆ ነበር፡፡

ቦርዱ የደረሰበት ጊዜያዊ ዕገዳ ለፓርቲዎች የሚሰጠውን ገንዘብ ለኦነን ከማስከልከል ጀምሮ እስከ ማሰረዝ ሊያደርስ እንደሚችል ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...