ሦስት ጓደኛሞች ምግብ ሊበሉ ሆቴል ይገቡና ሁለቱ እጃቸውን ሲታጠቡ፣ ጋብሮቩ ውድ የሆኑትን የምግብ ዓይነቶች ከዝርዝሩ ላይ በፍጥነት ይሰርዝ ጀመር፡፡
የሆቴሉ ባለቤት፣ በድርጊቱ ተገርመው አፍጠው ሲመለከቱትም ‹‹ሒሳቡን የምከፍለው እኔ ነኛ!›› አላቸው፡፡
*******
ቀድሞ የነበረበትን ዕዳ ያልከፈለው የአያ ሚንዮ ጐረቤት ሁለተኛ ብድር ሊጠይቅ ይሄዳል፡፡ ሽማግሌው ሚንዮም በትህትና ተቀብለውት ችግሩን ካዳመጡ በኋላ፣ እፊት ለፊቱ ያለውን ጠረጴዛ እያመለከቱ ከመሳቢያው ውስጥ የሚፈልገውን ያህል ገንዘብ እንዲወስድ ይፈቅዱለታል፡፡
ባለ ዕዳው መሳቢያውን ይጐረጉርና ‹‹አያ ሚንዮ! ለምን ይቀልዱብኛል? መሳቢያው ውስጥ ሰባራ ሳንቲም እንኳ የለም’ኮ!›› ይላቸዋል፡፡
ይኼኔ አዛውንቱ ሚንዮ፣ ‹‹አዬ ልጄ፣ የመጀመሪያውን ዕዳህን ሳትከፍል እንዴት ሰባራ ሳንቲም እኔ ዘንድ ሊኖር ይችላል ብለህ ነው?›› ሲሉ መለሱለት፡፡
- አረፈዓይኔ ሐጎስ፣ ‹‹ቀልዶች ከጋብሮቮ ምድር›› (1979)
*******