Sunday, October 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናፓርላማው ከቱርክ መንግሥት የተገኘ 6.3 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ አፀደቀ

ፓርላማው ከቱርክ መንግሥት የተገኘ 6.3 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ አፀደቀ

ቀን:

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባ ከቱርክ መንግሥት ለወታደራዊ ፋይናንስ የተደረገን ከ6.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አፀደቀ፡፡

በነሐሴ 2013 ዓ.ም. በቱርክ አንካራ በሁለቱ አገሮች የተደረገው የወታደራዊ ፋይናንስ ትብብር አንድ መቶ ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ ወይም በአሁኑ የምንዛሪ ዋጋ ወደ ዶላር ተቀይሮ ከ6.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚደርስ ሲሆን፣ በገንዘቡ የኢትዮጵያ መንግሥት ሙሉ በሙሉ ቱርክ ሠራሽ የሆኑ ወታደራዊ  ቁሳቁሶችን በአምስት ዓመት ውስጥ ከቱርክ ኩባንያዎች እንዲገዛ የሚያስገድድ መሆኑን በአዋጁ ተብራርቷል፡፡

ረቂቁ  መቅረቡን ተከትሎ፣ ቱርክ የፋይናንስ ድጋፍ ስታደርግ ከኢትዮጵያና ግብፅ ጋር ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ሊያሳድረው የሚችለው ጫና በደንብ ታይቷል ወይ? የሚል ከአባላቱ ጥያቄ አስነስቷል፡፡

በተለይም ዓለም በተለያየ ጎራ ተከፋፍሎ በተሠለፈበት በዚህ ወቅት ይህ የገንዘብ ድጋፍ አሁን ካለው ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ ጋር ምን ያክል ታይቷል? ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባል አቶ ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ናቸው፡፡

የመከላከያ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ለተነሱት ጥያቄዎች ማብራሪያ ሲሰጡ፣ እያንዳንዱ የአገሮች ግንኙነት ሌላ አካልን ለመጉዳት ታስቦ የሚደረግ ግንኙነት አይደለም፣ ‹‹ሁለቱ አገሮች የጋራ ጥቅም የሚያረጋግጡና የሚያስከብሩ ጉዳዮችን መሠረት አድርገው የፈጸሙት ስምምነት ነው፤›› ብለዋል፡፡

በመሆኑም ይህ ለአምስት ዓመታት የሚቆየው የገንዘብ ድጋፍ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተደረገ ስምምነት እንጂ ሦስተኛ ወገንን ለማስቆጣት ተብሎ የተደረገ ስምምነት አለመሆኑ ሊታወቅ ይገባል ሲሉ መልስ ሰጥተዋል፡፡

የአገር መከላከያን አቅም ለማሻሻል ከቱርክም ሆነ ከሌላ አካል ማግኘት የሚቻለውን እናገኛለን፡፡ ምንም እንኳ ሥጋቱ የማይተው ቢሆንም ከቱርክ ጋር አብራችሁ ስለሠራችሁ የእኔ ጠላት ናቸሁ የሚል አካል ካለ ጉዳዩ ሌላ ነው የሚሆነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

ምክር ቤቱ ከቱርክ መንግሥት ከተደረገው የገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ሁለቱ አገሮች በወታደራዊ መስክ፣ በትምህርት ሥልጠና በተናጠል ወይም በጋራ በሚያዘጋጁት ወታደራዊ ልምምዶች ለመካፈል፣ በመከላከያ ኢንዱስትሪ፣ በመከላከያ መረጃ ልውውጥ፣ በመከላያ መረጃ ሎጅስቲክ፣ በመከላከያ ጤና አገልግሎት፣ በኮሙዩኒኬሽን፣ አሌክትሮኒክስ፣ የመረጃ ሥርዓትና የሳይበር ጥቃት መከላከል ዘርፍ በጋራ ለመሥራት የተረገ ስምምነትና የአምስት ሚሊዮን የቱርክ ሊሬ በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈረመ የፋይናንስ ድጋፍ ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮልን አፅድቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...