Monday, October 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበሐረር ከተማ በተወረወረ ቦምብ ስምንት ሰዎች ጉዳት ደረሰባቸው

በሐረር ከተማ በተወረወረ ቦምብ ስምንት ሰዎች ጉዳት ደረሰባቸው

ቀን:

በሐረር ከተማ ሸንኮር ወረዳ፣ የሺ እመቤት ትምህርት ቤት አካባቢ በሚገኝ ዩዲ በተባለ ሆቴል ውስጥ ሲዝናኑ በነበሩ ሰዎች ላይ፣ በትንሳዔ በዓል ዕለት እሑድ ሚያዝያ 16 ቀን 2014 ዓ.ም. የትንሳዔ ዕለት በተወረወረ ቦንብ ስምንት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ከምሽቱ 2፡45 ላይ በሆቴሉ ወስጥ ተሰብስበው በነበሩ ሰዎች መሀል ቦምቡ መወርወሩን ለሪፖርተር የተናገሩት የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነስሪ ዘከርያ፣ ግለሰቦቹ ለሕክምና መወሰዳቸውን አስረድተዋል፡፡ እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ ግለሰቦቹ የደረሰባቸው ጉዳት ቀላልና ለሕይወታቸው አሥጊ ያልሆነ ሲሆን፣ ጉዳት ከደረሰባቸው ሰዎች ውስጥ አራቱ በማግሥቱ ሰኞ ሚያዝያ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. ከሆስፒታል ወደ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ ኮሚሽነር ነስሪ፣ ቀሪዎቹ አራት ግለሰቦች አሁንም በሕክምና ላይ መሆናቸውን ተናግረው፣ እግራቸው አካባቢ የደረሰባቸው የመቁሰል አደጋ ከባድ አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡

ጉዳዩ በምርመራ ላይ በመሆኑ የጥቃት አድራሾቹን ማንነት መናገር ከባድ መሆኑን የተናገሩት ኮሚሽነሩ፣ ከጥቃቱ በተያያዘ የተጠረጠሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ኮሚሽነር ነስሪ፣ ከዚህ አደጋ መከሰት በኋላ የተፈጠረ የሰላም መደፍረስ አለመኖሩን ተናግረው ‹‹ከሽብር ጋር ግንኙነት ይኑረው አይኑረው፣ መሬት ላይ በሌለና ባልተረጋገጠ ነገር መናገር ተገቢ አይደለም፡፡ በአንዳንድ ማኅበራዊ ሚድያዎች ደግሞ ዳግመኛ እንደተፈጠረ ሲናገሩ ነበር ሐሰትና ያልተረጋገጠ ነው፤›› ብለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...