Saturday, December 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ አውቶሞቢል ገዝተው ስም የማዞርና የተሽከርካሪ ሰሌዳ የማውጣቱን ኃላፊነት ለባለቤታቸው ሰጥተዋል]

  • እሺ ዛሬ ውሎሽ እንዴት ነበር?
  • ያው እንደተለመደው ነው?
  • እንደተለመደው ማለት?
  • ያው አንዱ ቢሮ ስሄድ እዚህ አይደለም እዚያኛው ነው ይላሉ። እዚያም ስሄድ እዚያኛው ነው ይላሉ…
  • ምንድነው ችግሩ?
  • እኔን ነው የጠየከኝ?
  • ሌላ ማን አለ?
  • ሚኒስትሩ አንተ ነህ ብዬ ነዋ?
  • እስኪ ነገር ማጣመሙን ትተሽ ተቋሙ የሚለውን ንገሪኝ ምን ችግር ገጠመኝ ነው የምትይው?
  • የተሽከርካሪ ሰሌዳ ነው ችግሩ። አቤት የሚጉላላው ሕዝብ ብዛቱ?
  • ስም ማዘዋወሩን ጨርሰሻል?
  • እሱማ ካለቀ ቆየ። የተሽከርካሪ ሰሌዳ ነው ማግኘት ያልታቻለው።
  • እንዴት የተሽከርካሪ ሰሌዳ ችግር ይፈጠራል?
  • እኔ ምን አውቄ ታርጋ ቁጥሩ የሚጻፍበት ሰማያዊ ቀለም የለም ነው የሚሉት?
  • ቀለም?
  • አዎ። ሰማያዊ ቀለም እጥረት በመፈጠሩ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ማተም አልተቻለም ነው የሚሉት።
  • እና ችግሩ መቼ ይፈታል አሉ?
  • ሲደርስ እንደውላለን ነው የሚሉት።
  • ወይ ጉድ?
  • እኔማ ቢቸግረኝ በሰሞኑ ቀለም ስጡን አልኳቸው?
  • የሰሞኑ ቀለም ደግሞ ምንድነው?
  • ግራጫ!

[ክቡር ሚኒስትሩ በፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያ የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ ከአማካሪያቸው ጋር እየተወያዩ ነው] 

  • ጤና ይስጥልኝ ክቡር ሚኒስትር ይኸው በቀጠሮአችን መሠረት ተገኝቻለሁ።
  • መልካም። የዛሬ አጀንዳችን የሚሆነው የፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያ ፕሮግራማችን ያስገኛቸውን ውጤቶች ለመዳሰስና ለተወካዮች ምክር ቤት በምናቀርበው ሪፖርት ውስጥ ቢካተቱ የምንላቸውን ለመለየት ነው።
  • ክቡር ሚኒስትር ለምክር ቤት የሚቀርበውን ሪፖርት ማዘግየት አይቻልም?
  • ለምን?
  • ወይም የፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያ ፕሮግራማችንን አፈጻጸም ብቻ ለሌላ ጊዜ ብናቆየውስ?
  • እንዴት ያልተሟላ ሪፖርት ይዘን እንቀርባለን? በዚያ ላይ የፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያ የተቋማችን ዓብይ ተግባር አይደለም እንዴ?
  • እሱማ ልክ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ታዲያ ምንድነው የምትለው?
  • ከፍተኛ ወቀሳ እንዳይቀርብብን ሠግቼ ነው?
  • የተገልጋዮች እርካታን በተመለከተ ሰሞኑን ያደረግነው ጥናት ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን አረጋግጧል ብላችሁ ሪፖርት አቅርባችሁ አልነበረም?
  • ልክ ነው ክቡር ሚኒስትር የተገልጋዮች እርካታ 80 በመቶ መሆኑን በጥናት አረጋግጠናል።
  • እና ምንድነው ያሠጋህ?
  • አንዱ ሥጋቴ በመቶኛ ያስቀመጥነውን የተገልጋዮች እርካታ ውጤት በቁጥር አስቀምጡ እንዳንባል ነው።
  • ቢባል ምን ችግር አለው?
  • የተገልጋዩቹን ብዛት በቁጥር ከተጠየቅን አነስተኛ ነው። ይህ ደግሞ ተቋማችንን ያስወቅሳል።
  • ስለዚህ እሱን በጥናቱ እንደቀረበው በመቶኛ እናስቀምጣለን።
  • የግድ በቁጥር ግለጹ ብንባልስ?
  • መቶኛም እኮ ቁጥር ነው እንላለን ካልሆነም…
  • ካልሆነ ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ጥናቱን ያካሄደው አማካሪ ውጤቱን ያቀረበው በመቶኛ ነው እንላለን።
  • እንደዛ ማለት ይቻላል?
  • ለምን አይቻልም?
  • አማካሪው ውጤቱን በቁጥር እንዲገልጽ እንዴት አላደረጋችሁም ተብለን ብንጠየቅስ?
  • በቁጥር እንዲገለጽ በጀት ስላልተያዘ ነው እንላለን።
  • እንደዛ ይቻላል?
  • ለምን አይቻልም?
  • እንዴት በጀት አልተያዘም ተብለን ብንጠየቅስ?
  • ከህልውና ዘመቻው ጋር በተያያዘ ነው እንላለን።
  • ከህልውና ዘመቻው ጋር ምን አገናኘው ብንባልስ?
  • በህልውና ዘመቻው ምክንያት ሁሉም ተቋማት በጀት እንዲቆጥቡ መንግሥት በማዘዙ መሆኑን እንገልጻለን።
  • እንደዛ ማድረግ ከተቻለ ጥሩ ነው። ነገር ግን…
  • ነገር ግን ምን?
  • አሁንም ሪፖርቱን ካላዘገየነው ከወቀሳ የምንድን አይመስለኝም፡፡
  • ለምን?
  • ምክንያቱም በፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያ ቃል ከገባናቸው በርካታ ጉዳዮች መካከል በዋናው ጉዳይ ላይ ምን ለውጥ አልመጣም።
  • ምን ነበር ዋናው ጉዳይ?
  • ሳናጣራ አናስርም፣ እያሰርን አንመረምርም የሚለው ነው።
  • እና ምንም የተገኘ ለውጥ የለም?
  • ምንም ለውጥ የለም ወደ እርስዎ ቢሮ ከመግባቴ በፊትም በዚህ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ወቀሳ ደርሶኛል።
  • የምን ወቀሳ! ማነው ያቀረበው?
  • የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ነው።
  • ምንድነው የሚሉት እነሱ ደግሞ?
  • በየአካባቢው ሰዎች ተይዘው እየተሰወሩ ነው። ቤተሰቦቻቸው ብቻ ሳይሆኑ የኮሚሽኑ መርማሪዎችም የታሰሩትን ዜጎች ፈልገው ማግኘት አልቻሉም ነው የሚለው።
  • የት የት ፈልግን ነው የሚለው ኮሚሽኑ?
  • በፌዴራልም ሆነ በየክልሉ የሕግ አስከባሪ ተቋማት ዞረን ማግኘት አልቻልንም ነው የሚለው ኮሚሽኑ።
  • እዚያ ምን አዞራቸው እነሱ?
  • ተጠርጣሪዎች የሚታሰሩት በነዚህ ተቋማት ስለሆነ ነዋ ክቡር ሚኒስትር?
  • በነዚህ ተቋማት ብቻ አይደለም፡፡
  • ከነዚህ ተቋማት ውጪ ሰዎችን የማሰር ሥልጣን ያለው ሌላ አካል አለ ክቡር ሚኒስትር?
  • በፍትሕ ዘርፍ ማሻሻያው ሌላ ተጨምሯል!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...