የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካን ወደነበረችበት ታላቅነት እመልሳለሁ ብለው ሥልጣን ከያዙ 50 ቀናትን ያስቆጠሩት ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ነው፡፡
በአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሥራ በጀመረ በመጀመሪያዎቹ 100 ቀናት ውስጥ በሕዝቡና በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የሚመዘንበት፣ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ለሕዝቡ ቃል የገባውን ለመተግበር ዕርምጃ የሚጀምርበት፣ ታላላቅ የሚባሉ ፕሬዚዳንታዊ ውሳኔዎችን የሚወስንበት፣ ለአሜሪካ ሕዝብ ጠቃሚ የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን የሚያሳውቅበትና በአጠቃላይም ለሕዝቡ ማንነቱን የሚያሳይበት ነው፡፡