አዲስ አበባ የዕውቀት ማከማቻና ማስተዳደሪያ ሥርዓት ባለቤት ልትሆን ነው
አዲስ አበባ በከተማዋ ካሉ ማነቆዎች አንዱ የሆነውን የመረጃ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችልና በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ተግባራዊ የሚሆን ‹‹የዕውቀት ማከማቻና ማስተዳደሪያ ሥርዓት›› ሊዘረጋላት ነው፡፡
ቅዳሜ ታኅሳስ 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ከሰንሻይን ኮንስትራክሽን ሕንፃ ላይ የወደቀ ሠራተኛ መሞቱ የግንባታ ደኅንነት ጥያቄዎችን በድጋሚ ቀሰቀሰ፡፡ አደጋው የደረሰው መስቀል አደባባይ አካባቢ በሚገነባ ትልቅ ሕንፃ ላይ ሲሆን፣ ሃያት ዲጀንሲ ሆቴል ከሚገነባበት አጠገብ መሆኑን ሪፖርተር በሥፍራው ተገኝቶ ታዝቧል፡፡
መለሰ አበራ የተባለ የ34 ዓመት ሠራተኛ በሕንፃው ላይ በሥራ ላይ በነበረበት ወቅት ወድቆ ሕይወቱ ያለፈ ሲሆን፣ ይህ በከተማይቱ ለግንባታ ደኅንነት የሚሰጠውን ትኩረት አናሳነት ያሳያል የሚሉ ተቃውሞዎች እንዲነሱ ምክንያት ሆኗል፡፡ በቅርቡ ልጅ እንደተወለደ የተነገረው መለሰ ከሕንፃው እንደወደቀ ሕይወቱ አልፏል፡፡