ፌዴራል ፖሊስ በአቶ ኢሳያስ ዳኘው ላይ ያቀረበው አቤቱታ ውድቅ ተደረገ
የፌዴራል ፖሊስ በአቶ ኢሳያስ ዳኘው ላይ ያቀረበውን የይግባኝ አቤቱታ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውደቅ አደረገው፡፡
ፍርድ ቤቱ አቶ ኢሳያስ ዳኘው የከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥረኛ ወንጀል ችሎት በ50 ሺሕ ብር ዋስትናና ከአገር እንዳይወጡ ዕግድ በመጣል ከእስር እንዲፈቱ የሰጠውን ትዕዛዝ አፀና፡፡
ፌዴራል ፖሊስ በአቶ ኢሳያስ ላይ ያቀረበውን የወንጀል ጥርጣሬ መነሻ ሐሳብ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትና ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ ያደረጉት ለሦስተኛ ጊዜ ነው፡፡