| 12 December 2018 በሕዝብ ስም መነገድ ነውር ነው! የአንድ አገርን ሕዝብ በብሔር ወይም በተለያዩ ማንነቶች በመከፋፈል በስሙ መነገድ የዘመናችን ልሂቃን መለያ ከሆነ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ከልዩነቶቹ ይልቅ የጋራ እሴቶቹና መስተጋብሮቹ የሚያመዝኑት ይህ ሕዝብ፣ በተለያዩ መልክዓ ምድሮችና የአየር ፀባዮች ውስጥ ቢኖርም ዕጣ ፈንታው ግን አንድ ነው፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 9 December 2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሆይ አብሮ መሥራትን ተለማመዱ! የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጡዘት ውጤት የሆነው መከፋፈል፣ መበታተንና እንዳይሆኑ ሆኖ መቅረት ምክንያቱ ጽንፈኝነት ነው፡፡ የተለያዩ ዓላማዎች ይዞ ለጋራ ጉዳይ አብሮ መሥራት ብርቅ የሆነበት የአገሪቱ ፖለቲከኞች ልማድ፣ ለጽንፈኝነት በጣም የተጋለጠ ከመሆኑ የተነሳ ከወዳጅነት ይልቅ ጠላትነትን ያበረታታል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 5 December 2018 ከግጭት ወደ ግጭት የሚደረገው ሽግግር ይብቃ! በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አሁንም ግጭቶች አሉ፡፡ ከግጭት ወደ ግጭት የሚደረገው ሽግግር መቋጫ ባለማግኘቱ፣ በተለያዩ ሥፍራዎች ግጭቶች እየተቀሰቀሱ የንፁኃን ደም እየፈሰሰ ነው፡፡ በሰላም ወጥቶ መግባት ከባድ በሆነባቸው ቦታዎች ንፁኃን ሕይወታቸውን በከንቱ እየገበሩ ነው፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 2 December 2018 መነሻን እንጂ መድረሻን አለማወቅ ለበለጠ ስህተት ይዳርጋል! በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የሚፈጸሙ ስህተቶች ሕዝብንም ሆነ አገርን ይጎዳሉ፡፡ ስህተቶቹ ሲደጋገሙ ደግሞ የጉዳታቸው መጠን ከመጨመሩም በላይ፣ አድማሳቸው እየሰፋ የአገርን ህልውና ይፈታተናሉ፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 28 November 2018 የፖለቲካ ምኅዳሩ የሚሰፋው መደማመጥ ሲኖር ነው! በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ትልቁ ችግር ለመነጋገርና ለመደማመጥ አለመፈላለግ ነው፡፡ ይህ ለዓመታት የዘለቀ ችግር ከበፊቱ የተሻለ አመቺ ሁኔታ ቢፈጠርለትም፣ አሁንም መተማመን ስለሌለ የጎሪጥ መተያየት ይስተዋላል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 25 November 2018 በቀጣዩ ምርጫ ላይ ለመነጋገር በአስተማማኝ ቁመና ላይ መገኘት ያስፈልጋል! ለሚቀጥለው ምርጫ ከወዲሁ ለመነጋገር እንደ መንደርደሪያ የሚሆን ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አገር ውስጥ ካሉና በቅርቡ ከውጭ ከገቡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ለመወያየት፣ ለማክሰኞ ኅዳር 18 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ይዘዋል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 21 November 2018 የተጠያቂነት ዳር ድንበር በግልጽ መሰመር አለበት! የመንግሥት አሠራር ለሕዝብ ተጠያቂነት እንዳለበት የተደነገገው በሕገ መንግሥቱ ነው፡፡ በወረቀት ላይ የሠፈረው ተግባራዊ ባለመሆኑ ግን የተጠያቂነት ዳር ድንበሩ አይታወቅም ነበር፡፡ የመንግሥት አሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት የሌለው እስኪመስል ድረስ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የአገር ሀብት ዝርፊያ ተፈጽሟል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 18 November 2018 የሚያዋጣው ለአገር ክብር በአንድነት መቆም ብቻ ነው! አገር ተከብራና ታፍራ ለዜጎቿ የምትመች መሆን የምትችለው ፍትሕ ሲሰፍን ነው፡፡ ፍትሕ በሌለበት ክብር የለም፣ አብሮነት አይታሰብም፣ ህልውናም ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 14 November 2018 በሕግ ያልተገራ ሥልጣን ለአስነዋሪ ድርጊቶች ይዳርጋል! የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግን መግለጫ በአንክሮ ለተከታተለ ማንም ሰው፣ በኢሕአዴግ ዘመን ተፈጸሙ የተባሉ ድርጊቶች በጣም ያስደነግጣሉ፡፡ በሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና በአገር ሀብት ዝርፊያ ላይ በተሰጠው ማብራሪያ፣ ወትሮ የሚታወቁት ኢትዮጵያዊ ጨዋነትንና የሞራል ልዕልናን ያዘቀጡ ድርጊቶች ተሰምተዋል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
| 11 November 2018 አጉል ጀብደኝነት የአገር ችግር አይፈታም! በበርካታ ችግሮች የተተበተበችው ኢትዮጵያ አሁንም ለበለጠ ችግር የሚዳርጋት ፈተና ከፊቷ ተጋርጧል፡፡ በማንነት፣ በአስተዳደራዊ ወሰንና በመሬት ይገባኛል እሰጥ አገባዎች ምክንያት በተለያዩ ክልሎች መካከል በሚከሰቱ አለመግባባቶች ግጭቶች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል፡፡ አሁንም ደም ለማፋሰስ የሚያደርሱ እሰጥ አገባዎች እየተሰሙ ነው፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ