ማኅበራዊ
ከተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በነፃ የተሰናበቱት...
- ለ18 ወራት በእስር ቆይተው በብቃት በመከላከላቸው ነፃ ወጥተዋል
የቀድሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ፋይናንሱን ከሚያመጡ ድርጅቶች ለመግዛት ባወጣው ዓለም አቀፍ የትራንስፎርመሮች ጨረታ ምክንያት፣ በሙስና ተጠርጥረው ክስ ተመሥርቶባቸው ለ18 ወራት ባደረጉት ክርክር በነፃ የተሰናበቱት ሁለት ምክትል ሥራ አስፈጻሚዎችና ሦስት ኃላፊዎች በሹመት ወደ ሥራቸው ተመለሱ፡፡
በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ የተነሳው እሳት...
- ሠራተኞቹ ቤተል ሆስፒታል ተኝተው እየታከሙ ነው
‹‹እሳቱ በማምረቻ ፋብሪካው ላይ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል›› ስኳር ኮርፖሬሽን
መጋቢት 5 ቀን 2007 ዓ.ም. ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት አካባቢ እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ በተነሳ ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ፣ አንድ የፋብሪካው ባለሙያ ሕይወታቸው ሲያልፍ በ16 ሠራተኞች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ታወቀ፡፡
ቦይንግ 767 አውሮፕላን በመጥለፍ የተከሰሰው...
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነውንና የበረራ ቁጥሩ ET-702 አውሮፕላን የካቲት 9 ቀን ለ10 አጥቢያ 2006 ዓ.ም. በመጥለፍ ወንጀል በሌለበት ክስ የተመሠረተበት ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ፣ መጋቢት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላለፈበት፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር ሕገወጥ ላላቸው...
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሕገወጥ መንገድ የመሬት ባለቤት ሆነዋል ላላቸው ነዋሪዎች፣ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በመስጠት ሕጋዊ ሊያደርጋቸው ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተገለጸ፡፡
ባለፉት ሰባት ወራት በፌዴራል ዳኞች...
በተያዘው በጀት ዓመት ያለፉት ሰባት ወራት ውስጥ ከ60 በላይ የዲሲፕሊን አቤቱታዎች በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በሚሠሩ ዳኞች ላይ ቀረቡ፡፡
በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የደረሰ...
- የደቡብ አፍሪካ ባለሙያዎች ድጋፍ ለመስጠት አዲስ አበባ ገቡ
በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ አካባቢ መሰንበቻውን የደረሰውን የሰደድ እሳት አደጋ ለማጥፋት ተንቀሳቅሰው ከነበሩት ባለሙያዎች መካከል በአንዱ ላይ የሞት፣ በሌሎቹ ሁለት ባለሙያዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደረሰ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከታተሏቸው የ830 ሚሊዮን...
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርብ ይከታተሏቸዋል የተባሉና በአጭር ጊዜ ተገንብተው ኮንዶሚንየም ቤቶችን እንደሚያገናኙ የሚጠበቁ የ830 ሚሊዮን ብር የመንገድ ግንባታ ውሎች ተፈረሙ፡፡
ተፈራ ደግፌ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ የባንክ...
(1918 – 2007 ዓ.ም.)
ባንክ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ‹‹ባንክ ኦፍ አቢሲኒያ›› ተብሎ ከተቋቋመበት በመቀጠል በ1923 ዓ.ም. የኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ በማስከተልም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቋቋም በመሪነት ተቀምጠው የነበሩት የውጭ አገር ዜጐች ነበሩ፡፡
ፈቃድ ያላቸው አጥፊዎች
ተስፋዬ የማነህ የሲኖትራክ አሽከርካሪ ሲሆን፣ የአሽከርካሪነት ሙያ የጀመረው ደግሞ በ18 ዓመቱ እንደሆነ ይናገራል፡፡ የቤት መኪና፣ ታክሲ፣ ኮብራ፣ አይሱዙና የከተማ አውቶቡስ አሽከርክሯል፡፡
ወተት ለተማሪዎች
በሰበታ ሙሉጌታ ገድለ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ከሚገኙ ተማሪዎች የተወሰኑት በየሜዳው በስፖርታዊ ጨዋታዎች ተጠምደዋል፡፡ ከፊሎቹ ደግሞ በተዘጋጀላቸው ዴስኮች ላይ ተቀምጠው ወተትና ዳቦ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
አሻራ ለማኖር
ተወልዶ ያደገው፣ የአንደኛና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለውና በሬዲዮ ኤሌክትሮኒክስ የሠለጠነው አዲስ አበባ ውስጥ ነው፡፡ ከሥልጠናውም በኋላ መርካቶ አካባቢ በቴክኒሽያንነት ሠርቷል፡፡
ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ለሥነ ሕዝብና ጤና...
ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ በየካቲት 2008 ዓ.ም. ለሚያካሂደው የሥነ ሕዝብና የጤና ዳሰሳ ጥናት ዕቅድ ለማዘጋጀት የሚያስችል ስምምነት መጋቢት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ከአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩኤስኤአይዲ) ጋር ተፈራረመ፡፡
የቄራዎችና ልኳንዳዎች ዘርፍ ማኅበር ተቋቋመ
የኢትዮጵያ አገር ውስጥ ቄራዎችና ልኳንዳዎች ዘርፍ ማኅበር መጋቢት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ተቋቋመ፡፡
‹‹ኮማኖየ›› – የጌዴኦ ጥንታዊ የሴቶች...
በሔኖክ ሥዩም
ዛሬ ላይ ብዙዎችን የሚያነጋግረው የሴቶች ጭቆናና ጥቂት ሥልጡን አገሮችን ደረት ያስነፋው የሴቶች መጠነኛ የኃይል /ሥልጣን/ ተጋሪነት እንደ እኛ ላሉ የቀደምት ሥልጣኔ ባለቤት ሕዝቦች የተደበላለቀ ስሜት ይፈጥርብን ይሆናል፡፡
የመጥፋት አደጋ ያንዣበበባቸው የኢትዮጵያ አንበሶች
የ‹‹ይሁዳ አንበሳ›› ቀዳማዊ ኃይለሥላሴን የወከለ መጠሪያ ነው፡፡ ታዋቂው የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኝ ቦብ ማርሌ የነፃነት ድምፅን ከሚያሰሙ ዘፈኖቹ በአንዱ ‹‹አይረን ላየን ዛየን›› እያለ አቀንቅኗል፡፡