Tag: ምሥረታ
በተከፈለ 5.9 ቢሊዮን ብር ካፒታል የተመሠረተው አማራ ባንክ
አማራ ባንክ አክሲዮን ማኅበር በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንደ አዲስ ታሪክ ሊጠቀስ የሚችለውን ከፍተኛ ካፒታልና ባለአክሲዮኖች ይዞ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ምሥረታውን ዕውን አድርጓል፡፡
‹‹ከአማራ ባንክ አክሲዮን የገዙ ሰዎች ቁጥር ከ155 ሺሕ በላይ ደርሷል›› አቶ መላኩ ፈንታ፣ የባንኩ አደራጅ ቦርድ ሰብሳቢ
ሥራ ሳይጀምር በሥራ ላይ ከሚገኙ ባንኮች የላቀውን የተከፈለ ካፒታል በማሰባሰብ ገበያውን እንደሚቀላቀል የሚጠበቀው አማራ ባንክ አክሲዮን ማኅበር፣ በሀብት አሰባሰብም ሆነ በባለአክሲዮኖች ብዛት ታሪካዊ ሊባል የሚችል ውጤት አስመዝግቧል፡፡
ጎህ ባንክ በ1.2 ቢሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል ተመሠረተ
በምሥረታ ላይ ከሚገኙ ባንኮች መካከል ጎህ ቤቶች ባንክ ወደ ሥራ ለመግባት የሚያስችለውን መሥራች ጉባዔ ማካሄዱን አስታወቀ፡፡
ባንኩ እንዳስታወቀው በ530 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታልና በ1.2 ቢሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል በይፋ ተመሥርቷል፡፡ ከሌሎች ባንኮች በተለየ በቤት ግንባታና በባንክ ንግድ ሥራዎች ላይ በማተኮር እንደሚንቀሳቀስ በማስታወቅ ወደ አክሲዮን ሽያጭ መግባቱ ይታወሳል፡፡
አማራ ባንክ የ400 ሚሊዮን ብር የአክሲዮን ድርሻ መሸጡን አስታወቀ
በቅርቡ የአክሲዮን ሽያጭ የጀመረውና በምሥረታ ላይ የሚገኘው አማራ ባንክ አክሲዮን ማኅበር፣ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን አክሲዮኖች መሸጡ ተገለጸ፡፡
Popular