Thursday, March 30, 2023

Tag: ስኳር ኮርፖሬሽን

የስኳር ኮርፖሬሽን ቦርድ ሜቴክ እጅ የቀሩ ሦስት የስኳር ፕሮጀክቶች ኮንትራት እንዲቋረጥ ወሰነ

የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ለዓመታት ሊያጠናቅቃቸው ያልቻላቸው ሦስት ግዙፍ የስኳር ፕሮጀክቶች የግንባታ ውሎች እንዲቋረጡ መወሰኑን፣ የፕሮጀክቶቹ ባለቤት የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡ ይኼንኑ ውሳኔም ኮርፖሬሽኑን የሚመራው ቦርድ እንዳፀደቀው ተገልጿል፡፡

ስኳር ኮርፖሬሽን ሜቴክ በያዛቸው ፕሮጀክቶች ላይ ዕርምጃ እንዳይወስድ በከፍተኛ አመራሮች ዛቻና ማስፈራሪያ ይደርሰው እንደነበር ገለጸ

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) የያዛቸውን አንዳንድ የስኳር ፕሮጀክቶች ውል በማቋረጥ ለማስቆም ሲሞከር የፕሮጀክቱን ባለቤት የስኳር ኮርፖሬሽን አመራሮች፣ ‹‹ይህ ማለት ከግንብ ጋር መጋጨት ነው፣ ወዮላችሁ አርፈችሁ ተቀመጡ፤›› የሚሉ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ሲደርሷቸው እንደነበር ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ እንዳወቅ አብቴ ይፋ አደረጉ።

ክሳቸው ያልተቋረጠ ተከሳሾች ቤተሰቦች አቤቱታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል

መንግሥት ይቅርታ በማድረግና ክስ በማቋረጥ ከግንቦት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ከ771 በላይ እስረኞች እንዲፈቱ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ፣ ክሳቸው ያልተቋረጠላቸው በርካታ እስረኞች ቤተሰቦች አቤቱታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል፡፡

ክሳቸው ከተቋረጠው የሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎች ጋር ታስረው የነበሩ ተከሳሾች ቅሬታቸውን ለመንግሥት አቀረቡ

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግና የአገሪቱ ርዕሰ ብሔር በአዋጅ የተሰጣቸውን ሥልጣን በመጠቀም በሙስና፣ በሽብርና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው የተከሰሱና ክርክራቸውን ጨርሰው ተፈርዶባቸው የነበሩ ግለሰቦች እንዲለቀቁ ሲያደርጉ፣ በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ በርካታ እስረኞች መታለፋቸው ቅሬታ እንዳደረባቸው ለመንግሥት አቤቱታቸውን አቀረቡ፡፡

በሙስና ምክንያት የታሰሩ ተከሳሾች ቤተሰቦች ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ አቤቱታ አቀረቡ

የልጆቻቸውን የትምህርት ቤትና የቤት ኪራይ መክፈል እንዳልቻሉ የሚናገሩ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸውና በማረሚያ ቤት የሚገኙ የስኳር ኮርፖሬሽን የተወሰኑ ታሳሪዎች ቤተሰቦች፣ በቅርቡ ለተሾሙት የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬም በአግባቡ ተቀብለውና አቤቱታቸውን ሰምተው ምላሽ እንደሚሰጧቸው በመንገር መልሰዋቸዋል፡፡

Popular

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...

የዓለም ኢኮኖሚ መናጋት ለወቅታዊው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 16...

የተዘነጋው የከተሞች ሥራ የመፍጠር ተልዕኮ

በንጉሥ ወዳጅነው አሁን አሁን የአገራችን የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አንገብጋቢና...

Subscribe

spot_imgspot_img