Tag: ቆዳ
በ200 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የሚገነባው የሞጆ ቆዳ ኢንዱስትሪ ማዕከል ለ30 ሺሕ ዜጎች ሥራ ይፈጥራል ተባለ
የኢትዮጵያን የቆዳ ልማት በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በአፍሪካ የቆዳ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ተምሳሌት ይሆናል የተባለውና በ200 ሚሊዮን ዶላር የሚገነባው የሞጆ የቆዳ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ከ30 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል ተባለ፡፡
አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ለኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪ የገበያ ዕድል ያመጣ ይሆን?
ኢትዮጵያ በቀንድ ሀብቷ ከዓለም አገሮች ከቀዳሚዎቹ አሥሩ አንዷ ስለመሆኗ ይጠቀሳል፡፡ ከአፍሪካም ከቀዳሚዎቹ ስለመሆኗም በተደጋጋሚ የሚገለጽ ነው፡፡ ይህንን ትልቅ ሀብት ግን በአግባቡ እየተጠቀመችበት አይደለም፡፡
ቆዳ ፋብሪካዎች ለውጭ ኩባንያዎች የተሰጠውን ዓይነት ማበረታቻና ድጋፍ ባለማግኘታቸው ከአምራችነት እየወጡ እንደሚገኙ ገለጹ
አገር በቀል የቆዳ ፋብሪካዎች ከመንግሥት ተገቢውን ድጋፍና ማበረታቻ ሊያገኙ ካለመቻላቸውም በላይ፣ የውጭ ባለሀብቶችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርግ አሠራር በመስፈኑ ህልውናቸው አደጋ ላይ መውደቁንና በርካቶችም ከኢንዱስትሪው ለመውጣት መገደዳቸውን አስታወቁ፡፡ ከ12 ያላነሱ ቆዳ ፋብሪካዎች በአቅም ዕጦትና በዕዳ መዘጋታቸው ተነግሯል፡፡
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል
ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመሸጋገር ጥረት ላይ ያለችው ኢትዮጵያ፣ የአምራች ኢንዱስትሪዋ አጣብቂኝ ውስጥ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
ይህ የተገለጸው የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአምራች ኢንዱስትሪውን የ2010 ዓ.ም. ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት ነው፡፡ ሐሙስ ነሐሴ 10 ቀን 2010 ዓ.ም.
በሞጆ ከተማ በ100 ሚሊዮን ዶላር የቆዳ ኢንዱስትሪ ዞን ሊገነባ ነው
ከአዲስ አበባ ከተማ 76 ኪሎ ሜትር ርቀት በኦሮሚያ ክልል ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በ100 ሚሊዮን ዶላር የቆዳ ኢንዱስትሪ ዞን ሊገነባ ነው፡፡
ለአካባቢያዊ ብክለት ከፍተኛ ድርሻ ያላቸውን የቆዳ ፋብሪካዎች አንድ ቦታ ለማሰባሰብ የታቀደው ከዓመታት በፊት ቢሆንም ዕቅዱ ተግባራዊ ሳይደረግ ቆይቷል፡፡ የኢትዮጵያ ቆዳና ቆዳ ውጤቶች ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንዱ ለገሠ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የፕሮጀክቱ ጥናት ከሦስት ዓመት በፊት ቢጠናቀቅም ገንዘብ ባለመገኘቱ ዘግይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በአነስተኛ ወለድ ብድር በመፍቀዱ ወደ ሥራ እየተገባ ነው ብለዋል፡፡
Popular