Tag: ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር
የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ኢትዮጵያ የተከተለችውን የቱሪስቶች የቆይታ ጊዜና የገቢ ስሌት ውድቅ አደረገ
በዚህ ዓመት የመጀመርያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ መንግሥት ከቱሪዝም ዘርፍ ከ1.8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታውቆ ነበር፡፡ ይሁንና ይህ ገቢ የተሰላበትን መንገድ ውድቅ የሚያደርጉ ትንታኔዎች ከዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ብቅ ብለዋል፡፡
የጥምቀት በዓልን በዩኔስኮ የማስመዝገብ ማመልከቻ ‹‹በመጋቢት›› ይገባል
በወርኃ ጥር የኢትዮጵያ አደባባዮች በበዓላት ደምቀው ይታዩበታል ከሚያሰኘው አንዱ የጥምቀት በዓል የሚከበርበት መሆኑ ነው፡፡ የውጭ ጸሐፍት ‹‹የአፍሪካው ኤጲፋኒያ›› (African Epiphany) በመባል በልዩ ልዩ ድርሳኖች የሚታወቀው የጥምቀት በዓልን በዩኔስኮ (የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት) በሰው ልጅ ወካይ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስነት ለማስመዝገብ (Representative List of Intangible Cultural Heritage of Humanity) የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን በይፋ እንቅስቃሴ ከጀመረ ከርሟል፡፡
ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ቅርሶችን በተሻለ ለማስጠበቅ የሚረዳ ሕግ እያረቀቀ እንደሚገኝ አስታወቀ
በአገሪቱ የሚገኙ ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ የተፈጥሮና ሌሎችም ቅርሶችን በተሻለ ክብካቤና በባለቤትነት ስሜት ለማስጠበቅ ያግዛል ያለውን የሕግ ረቂቅ ማዘጋጀት እንደጀመረ ያስታወቀው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ በቅርስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች ከሚገኘው ገቢ እስከ 30 በመቶ እንዲደርሳቸው ማቀዱን ይፋ አድርጓል፡፡
የኮከብ ምደባ ከተካሄደባቸው 365 ሆቴሎች ውስጥ አስገዳጅ መሥፈርት ያሟሉት 167 ብቻ መሆናቸው ታወቀ
የፖለቲካ ቀውሱ የቱሪስት ፍሰቱን አልገታም ተብሏል
ከሦስት ዓመት በፊት በወጣውና ካቻምና በ365 ሆቴሎች ላይ በተደረገ የኮከብ ደረጃ ምደባ መሠረት ተገቢውን መሥፈርት በማሟላት ደረጃ ያገኙት ሆቴሎች 135 ብቻ እንደሆኑ ታወቀ፡፡ አብዛኞቹ የንፅህና፣ የአደጋ ጊዜ መውጫና ሌሎችም አስገዳጅ መሥፈርቶችን ማሟላት ባለመቻላቸው ነው ተብሏል፡፡
ዮድ አቢሲኒያ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብኛል የሚል አቤቱታ ለመንግሥት አቀረበ
ጥርጣሬውን ወደ አቶ ሰይፉ ፋንታሁን ማድረጉን ሰነዶች ይጠቁማሉ
የብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ እሴቶችን በማስተዋወቅ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ታዋቂ በመሆን ‹‹የኢትዮጵያ የባህል አምባሳደር›› ተብሎ በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የተሰየመው ዮድ አቢሲኒያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ‹‹የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብኛል›› በማለት አቤቱታ ለሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ማቅረቡ ታወቀ፡፡
Popular
በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው
(ክፍል አራት)
በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ)
ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...
ለመጪው ዓመት የሚያስፈልገው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይጠይቃል
ለመጪው 2016 ዓ.ም. ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ለታቀደው 4.3...