Tag: ኃይለ ማርያም ደሳለኝ
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በክብር ተሸኙ
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ባለቤታቸው ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ በሥልጣን ዘመናቸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ በይፋ የክብር አሸኛኘት ተደረገላቸው፡፡ አቶ ኃይለ ማርያም አገሪቱ ከፍተኛ ደረጃ ያለው የክብር ሜዳሊያና ዲፕሎማ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ተበረከተላቸው፡፡
‹‹እኛ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ ይገባናል ያስፈልገናል››
ሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን በመተካት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሰየሙት ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲና ነፃነት የሚያስፈልግ ብቻ ሳይሆን የሚገባ እንደሆነ ተናገሩ፡፡
‹‹እኛ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ ይገባናል፣ ያስፈልገናል፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ፣ ‹‹ዴሞክራሲ ያለ ነፃነት አይታሰብም፣ ነፃነት ደግሞ ከመንግሥት ለሕዝብ የሚበረከት ስጦታ አይደለም፤›› ሲሉ ለፓርላማ አባላትና በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት ለተከታተሉ ኢትዮጵያውያን ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሰየሙ
መጋቢት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) ሊቀመንበር በመሆን የተመረጡት ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተሰየሙ፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ከተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትር ብዙ ይጠብቃል!
ኢትዮጵያ በታሪኳ በውስጥ ችግር ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ከገባችባቸው ጊዜያት መካከል እንዳሁኑ የከበደ የለም፡፡ ላለፉት ሦስት ዓመታት ያህል ሰላምና መረጋጋት ደፍርሶ የበርካቶች ሕይወት ከማለፉም በላይ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ በተለያዩ ግጭቶች ሳቢያ ተፈናቅለዋል፡፡ የአካልና የሥነ ልቦና ጉዳት የደረሰባቸውም በርካቶች ናቸው፡፡ መጠኑ የማይታወቅ የአገር ሀብት ወድሟል፡፡ በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት ሳቢያም አገር ቋፍ ላይ ትገኛለች፡፡
ፓርላማው ከዕረፍት መልስ መደበኛ ስብሰባውን ሐሙስ ይጀምራል
የ2010 ዓ.ም ግማሽ የሥራ ዘመኑን መጠናቀቅ ተከትሎ ለዕረፍት ዝግ ሆኖ የከረመው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከአንድ ወር በኋላ መደበኛ ስብሰባውን ከሐሙስ መጋቢት 6 ቀን 2010 ዓ.ም. እንደሚጀምር የምክር ቤቱ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡
Popular
መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...
በሰጥቶ መቀበል መርህ መደራደርና ሰላም ማስፈን ለምን ያቅታል?
በያሲን ባህሩ
አገር ግንባታ የትውልድን ትልቅና ታሪካዊ ኃላፊነት የሚጠይቅ ተግባር...