Tag: አረጋውያን
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቄዶንያ ሕንፃ ሊገነባ ነው
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፓይለቶች ለመቄዶኒያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል አሥር ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል ገቡ፡፡ የአየር መንገዱን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያምን ጨምሮ ከአንድ ሺሕ በላይ ፓይለቶች እያንዳንዳቸው ከኪሳቸው አሥር ሺሕ ብር በማዋጣት ነው ድርጅቱ ለመርዳት ቃል የገቡት፡፡ ከቀናት በፊትም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለመቄዶኒያ ሁለት አምቡላንሶች መለገሱ የሚታወስ ነው፡፡
በአዲስ አበባ አብዛኞቹ አረጋውያን የምግብ እጥረት ይገጥማቸዋል
በአዲስ አበባ ከተማ 74 ከመቶ የሚሆኑት አረጋውያን ለከፍተኛ፣ እንዲሁም 97 ከመቶ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ መዳረሻ የምግብ እጥረት እንደሚገጥማቸው ተነገረ፡፡
‹‹የመገናኛ ብዙኃን ትኩረት ለአረጋውያን›› በሚል ርዕስ ታኅሣሥ 12 ቀን 2010 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ጡረተኛና አረጋውያን ብሔራዊ ማኅበር ባካሄደው ዓውደ ጥናት ላይ እንደተመለከተው፣ ለምግብ እጥረቱ የቤተሰብና የማኅበረሰብ ድጋፍ አናሳ መሆን እንደምክንያት ተጠቅሷል፡፡
Popular