Tag: ኪን
የሞርጋን ቤተሰብ በልደት ዋዜማ
‹‹ሙዚቃ በየምንሔድበት አገር እናቀርባለን፡፡ ወደ ኢትዮጵያ በዚህ የበዓል ወቅት መምጣት ግን ሙዚቃ ከማቅረብም በላይ ነው፡፡ ለገና በዓል በኢትዮጵያ መገኘታችን ታላቅ ደስታ ሰጥቶናል፤›› በማለት ነበር የሞርጋን ሔሪቴጅ ባንድ ወንድማማቾች የተናገሩት፡፡ በልደት በዓል ዋዜማ በኤቪ ክለብ ሙዚቃዎቻቸውን ለማስደመጥ ከናይሮቢ፣ ኬንያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡
የሠዓሊቷ ጉዞ በሦስቱ መንግሥታት
ከወራት በፊት፣ ሠዓሊት ደስታ ሐጎስ ስቱዲዮዋ ውስጥ ጋዋን ለብሳ፣ ሸራተን አዲስ በየዓመቱ ለሚያካሂደው ‹‹አርት ኦፍ ኢትዮጵያ›› ዐውደ ርዕይ አሥረኛ ዙር የሚሆን ሥዕል እያዘጋጀች ነበር፡፡ ተንቀሳቃሽ ስልኳ ሲጠራ እጇ ላይ ያለውን ቀለም በጋዋኗ ጠርጋ አነሳች፡፡ የተደወለላት ከአምስት አሠርታት በላይ በሥነ ጥበቡ ላበረከተችው አስተዋፅኦ እውቅና እንደሚሰጣት ለመግለጽ ነበር፡፡ አንድ የሽልማት ድርጅት በሥዕልና ቅርፃ ቅርፅ ዘርፍ የዕድሜ ዘመን የሥዕል የከፍተኛ ክብር ተሸላሚ መሆኗን የሚያበስር ደብዳቤም ላከላት፡፡
በታሪክ ነገራ ላይ ያተኮረው የፊልም ፌስቲቫል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር 12ኛውን የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል (ኢትዮ ፌስት) መክፈቻ ለማስተናገድ መዘጋጀቱን ከሩቅ የሚታዩት ባነሮች ይናገራሉ፡፡ ‹‹ሳንኮፋ፣ የታሪክ አተራረክ ጥበብ›› በሚል የሚከናወነውን ፌስቲቫል የሚያስተዋውቁ ፖስተሮች በብሔራዊ አካባቢ በሚገኙ ምሰሶዎች ላይም ተለጥፈዋል፡፡ ከታኅሣሥ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ለሰባት ቀናት የሚቆየው ፌስቲቫሉ በብሔራዊ ቴአትር የተከፈተው አመሻሽ ላይ ነበር፡፡
ሰሎሞን ዴሬሳ!
በቅርቡ በ80 ዓመቱ ዜና ዕረፍቱ የተሰማው፣ በዘርፈ ብዙ ዕውቀቱ ተጠቃሽ የነበረው ዕውቁ ገጣሚና ጸሐፊ፣ ጋዜጠኛና የፍልስፍና መምህር ሰሎሞን ዴሬሳ ሥርዓተ ቀብሩ ጥቅምት 25 ቀን 2010 ዓ.ም. በሚኔሶታ ከተማ በግብአተ እሳት መፈጸሙ ይታወሳል፡፡ ነፍስ ኄር ሰሎሞን ዴሬሳ ከ19 ዓመታት በፊት (መስከረም 1991 ዓ.ም.) ከሪፖርተር መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተር (በወቅቱ) ገዛኸኝ ጌታቸው ጋር ቃለ ምልልስ አድርጎ ነበር፡፡
Popular