Tag: ኮሌራ
በአዲስ አበባ የኮሌራ ክትባት ተጀመረበአዲስ አበባ የኮሌራ ክትባት ተጀመረ
በአዲስ አበባ ለኮሌራ ወረርሽኝ ተጋላጭነት ላላቸው 17,000 ያህል ሰዎች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት መስጠት ተጀመረ፡፡ የኢቦላ ወረርሽኝም ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ከ500 በላይ ሰዎች በኮሌራ ተጠቅተዋል
በአገር አቀፍ ደረጃ 525 ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ ሲጠቁ 16 ሰዎች ደግሞ በበሽታው መሞታቸውን የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ከፍተኛ ተጋላጭነት ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች የኮሌራ በሽታ መከላከያ ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በቀጣይ ቀናት እንደሚካሄድና ክትባቱ ሙሉ ለሙሉ ወረርሽኙን መከላከል እንደማያስችል ተገልጿል፡፡
በኮሌራ ወረርሽኝ 15 ሰዎች ሲሞቱ ከ300 በላይ በበሽታው ተይዘዋል
በአራት ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ በኮሌራ ወረርሽኝ 15 ሰዎች ሲሞቱ 390 ሰዎች በወረርሽኝ መያዛቸውን፣ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
በተከሰተው የኮሌራ በሽታ በኦሮሚያ ክልል አንድ፣ በአማራ ክልል 14 ሲሞቱ፣ ትግራይና ሶማሌን ጨምሮ 390 ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸውን ኢንስቲትዩቱ አስረድቷል፡፡
Popular