Tag: የዓለም ዋንጫ
ከሚጠበቀው በታች የተጎበኘው የዓለም ዋንጫ ወደ ኬንያ አምርቷል
የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ከኮካ ኮላ ኩባንያ ጋር በመተባበር ከ50 በላይ አገሮች እንዲጎበኝ ዕቅድ የተያዘለት የዓለም ዋንጫ የአዲስ አበባ ቆይታውን አጠናቆ ወደ ኬንያ ናይሮቢ አምርቷል፡፡
126 ሺሕ ኪሎ ሜትር የሚጓዘው የዓለም ዋንጫ የካቲት 17 አዲስ አበባ ይገባል
ብዙዎች የሚመኙት፣ ነገር ግን ጥቂቶች በአራት ዓመት አንድ ጊዜ የሚታደሙበት የዓለም ዋንጫ ዝግጅት በብዙ ውጣ ውረድ የአዘጋጅነቱን ዕድል ባገኘችው ሩሲያ በመጪው ክረምት ይካሄዳል፡፡ በእግር ኳሱ 32 የዓለም ኃያላን የሚፎካከሩበት የዓለም ዋንጫ፣ ከዚያ በፊት ከ50 በላይ አገሮች እንዲጎበኝ በተያዘለት ፕሮግራም መሠረት ቅዳሜ የካቲት 17 ቀን 2010 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል፡፡
የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ከኮካ ኮላ ኩባንያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የዓለም ዋንጫ ጉብኝት፣ በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአሥር አገሮች የጉብኝት ፕሮግራም ተይዞለታል፡፡ የአዘጋጇ ሩሲያ 35 ከተሞችን ጨምሮ ከ50 በላይ በተመረጡ የዓለም አገሮች ይንቀሳቀሳል ተብሏል፡፡
Popular