Tag: ዶፒንግ
የዓለም አቀፍ ፀረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ ኢትዮጵያን አደነቀ
የዓለም አቀፍ ፀረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ (ዋዳ) ኢትዮጵያ በዘርፉ እያደረገች ያለውን ቁጥጥርና ክትትል እንዲሁም በዚሁ እያስመዘገበች ያለውን ውጤት አደነቀ፡፡ አገሪቱ ለዋዳ ፀረ አበረታች ቅመሞች ዘመቻና ለሦስትዮሽ ፕሮግራሞች ትክክለኛ ማሳያ መሆኗን የዋዳ ምክትል ዳይሬክተር ሮበርት ኮህለር ገልጸዋል፡፡
የዓለም አቀፍ ፀረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ፣ ኢትዮጵያ በተለይ በአትሌቲክሱ ዓለም ላይ ያላትን የበላይነት ግምት ውስጥ በማስገባት አበረታች ቅመኞች በይበልጥ ይመለከታቸዋል በሚል ለይቶ ካስቀመጣቸው አምስት አገሮች አንዷ አድርጎ ሲመለከታት ቆይቷል፡፡ በዚሁ መነሻነት ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ችግሩን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ በተለይም ካለፈው ዓመት ጀምሮ፣ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት በማቋቋም እንቅስቃሴ ስታደርግ መቆየቷ አይዘነጋም፡፡
Popular