Tag: ግጭት
የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በአገሪቱ የፀጥታ ጉዳይ ላይ እየመከረ ነው
ሰላሳ ስድስት አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰብሰባ፣ በአገሪቱ የፀጥታ ጉዳይ ላይ እየመከረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የሪፖርተር ምንጮች እንደጠቆሙት የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ ማክሰኞ ታኅሳስ 3 ቀን 2010 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ የተጀመረ ሲሆን፣ በዋናነት አገሪቱ ባጋጠማት የፀጥታ ጉዳይ ላይ እየመከረ መሆኑ ታውቋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች የግጭት ዓውደ ግንባር አይሁኑ!
የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ከበፊት ጀምሮ የኢትዮጵያውያን ሁነኛ መገናኛ ሥፍራ በመሆናቸው ‹‹ትንሿ ኢትዮጵያ›› በመባል ይታወቃሉ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ ለጋ ወጣቶች ከአራቱም ማዕዘናት የሚገናኙባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ብሔር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ እምነት፣ ወዘተ. ተቻችለውባቸው የመማር ማስተማር መርሐ ግብራቸውን ሲያከናውኑ ነው የሚታወቁት፡፡
በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተቀሰቀሰው የተማሪዎች ግጭት ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተዛምቷል
የሦስት ተማሪዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ20 በላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል
በትግራይ ክልል በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተቀሰቀሰ ግጭት ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች መዛመቱ ተገለጸ፡፡ በሕይወትና በአካል ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡
በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት አንድ ተማሪ ሲሞት፣ ከ20 በላይ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ዩኒቨርሲቲም በተመሳሳይ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ተማሪዎች ሕይወታቸው ማለፉን፣ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ አስታውቀዋል፡፡
በደቡብ ኦሞ ዞን ለበርካቶች ሞት ተጠርጣሪ የሆኑ 11 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ሰኞ ኅዳር 25 ቀን 2010 ዓ.ም. ከረፋዱ አሥር ሰዓት ጀምሮ በተፈጠረ ግጭት፣ ለበርካቶች ሕይወት መጥፋት ተጠያቂ ናቸው የተባሉ 11 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ፡፡
ደም አፋሳሽ ግጭቶች የፌዴራል ሥርዓቱ ውጤት አለመሆናቸውን ለመተንተን ውይይት ተጀመረ
በተለያዩ ክልሎች የተከሰቱ ደም አፋሳሽ ግጭቶች ‹‹የፌዴራል ሥርዓቱ ውጤቶች ናቸው›› ለሚሉ አካላት ምላሽ ለመስጠት፣ መንግሥት የፖለቲካ አመራሩንና ሠራተኞችን ማወያየት ጀመረ፡፡
በፌዴራል መንግሥት ደረጃ 80 ገጾች ያሉትና በአምስት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሰነድ ተዘጋጅቶ ለአወያይ አመራሮች ተበትኗል፡፡
Popular