Friday, December 1, 2023

Tag: ፌዴራል መንግሥት

የፌዴራል መንግሥት በውክልና የወሰደውን የአዲስ አበባ ገቢዎች ባለሥልጣን መልሶ አስረከበ

የፌዴራል መንግሥት በውክልና ተረክቦ ያስተዳድር የነበረውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለሥልጣን መልሶ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስረከበ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው ረቡዕ ታኅሳስ 18 ቀን 2010 ዓ.ም. ከአምስት ዓመታት በላይ ተለይቶ የቆየውን የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ባለሥልጣንን፣ ከኢትዮጵያ ጉምሩክና ገቢዎች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሞገስ ባልቻ ተረክበዋል፡፡

ፓርላማው በ13 ድምፀ ተአቅቦ የደን ልማት ጥበቃ አዋጅን አፀደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢሕገ መንግሥታዊ ነው የሚል ክርክር የቀረበበትን የደን ልማት ጥበቃና አጠቃቀም አዋጅ በ13 ድምፀ ተአቅቦ አፀደቀ፡፡ ኢሕአዴግ በሚመራበት ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መርህ መሠረት የፓርላማ አባላት ከፓርቲው የበላይ አካል የተሰጡ ውሳኔዎችን መቃወም እንደ ዲስፕሊን ጥሰት የሚቆጠር በመሆኑ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ የተቃውሞ ክርክር ያቀረቡ አባላትና ሌሎችም በተቃውሞ ድምፅ ከመስጠት ይልቅ ድምፅ ተአቅቦ ማድረግን መርጠዋል፡፡ አንድ ረቂቅ አዋጅ በ13 የኢሕአዴግ አባላት ድምፅ ተአቅቦ ሲፀድቅም የመጀመርያው ሊሆን እንደሚችል ቅርበት ያላቸው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

መንግሥት የሚከበረው ሕዝብን አክብሮ ሲያስከብር ነው!

ሕዝብና መንግሥት ሆድና ጀርባ ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች መካከል አንደኛው የግልጽነት መጥፋት ነው፡፡ ግልጽነት ሲጠፋ መተማመን አይኖርም፡፡ መተማመን በሌለበት መከባበር አይታሰብም፡፡ መከባበር ከቤተሰብ ይጀምራል፡፡ ከዚያም ወደ ጎረቤት ተሻግሮ ወደ ማኅበረሰቡ ይደርሳል፡፡ በዚህ መሠረት መራመድ ሲቻል በአገር ደረጃ መከባበር ባህል ይሆናል፡፡

የዜጎችን ደኅንነት ማስጠበቅ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ግዴታ ነው!

ኢትዮጵያውያን በመረጡበት ሥፍራ የመኖር፣ የመሥራት፣ የመዘዋወርና ሀብት የማፍራት መብታቸው በሕግ የተረጋገጠ ቢሆንም ተግባራዊ ባለመሆኑ ብቻ፣ በበርካታ ዜጎቻችን ላይ ከፍተኛ በደል ተፈጽሟል፡፡ ዜጎች በገዛ አገራቸው ‹‹መጤ›› እየተባሉ ጥቃት ሲፈጸምባቸው፣ ሲፈናቀሉና ሲገደሉ በተደጋጋሚ ጊዜያት ታይቷል፡፡

የመሠረተ ልማት ተቋማት በቅንጅት ለመሥራት ተስማሙ

ኢትዮ ቴሌኮም በዚህ ዓመት 700 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ዝርጋታ ያካሄዳል በፌዴራል መንግሥትና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ የመሠረተ ልማት ተቋማት፣ ከዚህ በኋላ በአዲስ አበባ የሚያከናውኗቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በመናበብ ለመገንባት ረቡዕ ጥቅምት 29 ቀን 2010 ዓ.ም. የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

Popular

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...

Subscribe

spot_imgspot_img