ሠራተኞችን ወደ ዓረብ አገሮች ለመላክ መንግሥታት ስምምነት ቢፈጽሙም አስፈጻሚው ግራ እያጋባቸው መሆኑን ኤጀንሲዎች ገለጹ
በተለያዩ የሥራ መስኮች ሠራተኞችን ወደ ዓረብ አገሮች ለመላክ በኢትዮጵያ መንግሥትና በአራት የዓረብ አገሮች መንግሥታት መካከል ስምምነት ተደርጎ በየፓርላማቸው የፀደቀ ቢሆንም፣ አስፈጻሚው የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ግራ እያጋባቸው መሆኑን የውጭ ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ገለጹ፡፡