አቶ ኢሳያስ ዳኘው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በሰባት አባላት በፀደቀ ውሳኔ ሊጠየቁ እንደማይገባ ተናገሩ
የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት የሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ወንድም አቶ ኢሳያስ ዳኘው፣ ኢዲኤም ለተባለ የአሜሪካ አማካሪ ድርጅት ከተፈጸመ ክፍያ ጋር በተያያዘ በሙስና መጠርጠራቸውን ተቃወሙ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጨምሮ በሰባት አባላት በፀደቀ ውሳኔና በተፈጸመ ክፍያ እሳቸው ሊጠየቁ እንደማይገባም ገልጸዋል፡፡