Tuesday, November 28, 2023

Author Name

ዘመኑ ተናኘ

Total Articles by the Author

262 ARTICLE

የኢትዮጵያና የኤርትራ የወደፊት ተስፋና የወቅቱ ፈተና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሲሰየሙ ባደረጉት ንግግር ከጠቀሷቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታትን ግንኙነት የተመለከተ ነበር፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ ጅግጅጋ አመራ

በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የተመራ የልዑካን ቡድን ቅዳሜ መጋቢት 29 ቀን 2010 ዓ.ም. በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች ድንበር አካባቢ ላይ ተከስቶ የነበረውን ግጭት በዘላቂነት ለመፍታት ወደ ጅግጅግ አቅንቷል፡፡

በሱዳን ሲካሄድ የነበረው የሚኒስትሮች ስብሰባ ያለውጤት ተበተነ

የኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የውጭ ጉዳይና የውኃ ሀብት ሚኒስትሮች በህዳሴ ግድቡ ውኃ አሞላልና አለቃቀቅ እንዲሁም የግድቡን አካባቢያዊ ተፅዕኖን በተመለከተ በሱዳን ካርቱም ከመጋቢት 26 እስከ 27...

በህዳሴ ግድቡ ላይ የሚደረገው ውይይት በተያዘለት ቀነ ቀጠሮ ይካሄዳል

ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን በህዳሴ ግድቡ ላይ የሚያደርጉት ውይይት በተያዘለት ቀነ ቀጠሮ እንደሚካሄድ ታወቀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ሦስቱ አገሮች በህዳሴ ግድቡ ላይ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ከመጋቢት 26 እስከ 27 ቀን 2010 ዓ.ም. ውይይት ለማድረግ ቀነ ቀጠሮ ይዘዋል፡፡ ሦስቱ አገሮች የሚያደርጉት ውይይትም በተያዘለት ቀን እንደሚካሄድ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የምትደራደረው ባድመ ከተመለሰላት ብቻ እንደሆነ አስታወቀች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያላትን የፖለቲካ ልዩነት በማጥበብ ልትደራደር የምትችለው፣ ባድመ ከተመለሰላት ብቻ እንደሆነ አስታወቀች፡፡ የኤርትራ መንግሥት ይህን ያለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተሰየሙ በኋላ፣ ባደረጉት ንግግር ለኤርትራ መንግሥት ላቀረቡት ጥሪ በሰጠው ምላሽ ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገቡትን ቃል ተግባር ላይ እንዲያውሉ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በፓርላማ በተሰየሙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ ለሕዝብ የገቡትን ቃል በተግባር እንዲያውሉ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ፡፡  

ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር በሁሉም ክልሎች ሕዝባዊ ውይይቶች ሊካሄዱ ነው

በአገሪቱ ላለፉት ሦስት ዓመታት ያህል የተከሰተውን ችግር ለመቅረፍና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር፣ በሁሉም ክልሎች ሕዝባዊ ውይይቶች ሊካሄዱ እንደሆነ ታወቀ፡፡ የኢሕአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ከተጠናቀቀ በኋላ በመላ አገሪቱ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠርና በየአካባቢው የሚፈጠሩ ችግሮችን ለማስወገድ፣ በሁሉም ክልሎች ሕዝባዊ ውይይቶች እንዲካሄዱ ውሳኔ መተላለፉን አንድ የኢሕአዴግ የምክር ቤት አባል ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ውኃ የሚይዝበትን ቀን ለግብፅና ለሱዳን ማሳወቋ ተሰማ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለ ሰባተኛ ዓመት ላይ፣ ኢትዮጵያ የግድቡ ውኃ የሚይዝበትን ቀን ለግብፅና ለሱዳን ማሳወቋ ተሰማ፡፡ የውጭ ጉዳይ፣ የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊዎች ለሪፖርተር እንዳረጋገጡት፣ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡ ሙሌት መቼ እንደሚጀመር ለግብፅና ለሱዳን አስታውቃለች፡፡

‹‹የሥልጣን ፍላጎት ለጥቅም ቡድኖች መፈጠርና መሻኮት የተመቸ ሆኗል›› የኢሕአዴግ ምክር ቤት

የኢሕአዴግ ብሔራዊ ምክር ቤት ዓርብ መጋቢት 21 ቀን 2010 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ አገሪቱ ወደ ቀውስ እንድትገባና አገራዊ ህልውናን የመፈታተን ጠንቅ ያጋጠመበት አንዱ ምክንያት፣ የሥልጣን ፍላጎት ለጥቅም ቡድኖች መፈጠርና መሻኮት የተመቸ ሁኔታ በመፍጠሩ እንደሆነ አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ፖሊሲ እንድታወጣ ተጠየቀ

በኢትዮጵያ የሚስተዋለው የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በችግሮች የተተበተበ ስለሆነ፣ ችግሮቹን ለመፍታት መንግሥት የአጠቃቀም ፖሊሲ እንዲያወጣ ተጠየቀ፡፡ ይህ ጥያቄ የቀረበው ከሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ከተውጣጡ ወጣቶች ሐሙስ መጋቢት 20 ቀን 2010 ዓ.ም. በጁፒተር ሆቴል የፓናል ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡

Popular